Sheik Husen Gibreel
Contents | ማውጫ

Sheik Hussen Warned Us To Stay Away From Shirk | Prophecy of Sheik Hussen Gibril

አደራ ፡ ባለማወቅ እንዳታሻርኩ ፡ ብለዋል | ሼህ ሁሴን ጅብሪል

      ...አደራ ብያለሁ ፡ ደግሜ ደግሜ
      ተመሄደ በፊት ፡ በሞት ተቀድሜ...
      ...ሁሴን ስጠኝ ብለህ ፡ አትምጣ አጠገቤ
      ሰጩም ነሹም አላህ ፡ ልንገርህ ተልቤ...
      ...እስቲ አላህን ፍራ ፡ አታጎንብስ ለኔ
      ለሰው እንዳሰግዱ ፡ ረግሚያለሁ እኔ...
    

በኢትዮጵያ ውስጥ ፡ ለወልዮች ተመቃብራቸው ላይ ፡ ፍየል ይታረዳል ፡ ሰው ይነዘርባቸዋል ፡ ሞተውም ልክ በሂወት እንዳሉ ፡ ሰው ጀባታ የሰጣቸዋል ፣ እኔም ካያታቸን ፡ ሽህ ሁሴን ጅብሪል ዘንድ ፡ ወሎ ሄጄ ፡ ባይኔ ያየሁት ፡ ነገር ነው። እሳቸው ግን ፡ ከመሞታቸው በፊት ፡ ይሄን እንዳታረጉ ፡ ብለውን ሄደዋል። ሕዝባችን ግን ፡ በዚህ አይስማማም ፣ እንዳውም ይሄንን ተተቃወምክ ፡ ሊጣሉህም ይችላሉ ፣ ጌታው ሸህ ሁሴን ጅብሪል ፡ በማነኛውም በሞተ ሰው ፡ እንዳትመጀኑ ሲሉ አስጠንቅቀዋል ፣ እንዳውም ከዘመዶቻችን ፡ አንዱን ሰው ፡ እኔም ሙክት ፡ ገዝቸ ስለነበር ፡ ለምን ለሳቸው ብለን ፡ ሶደቃ ነይተን ፡ ብናርደውና ቢበላ ፡ ምን አለው? ብየ ብጠይቀው ፡ ቤተሰቡ እንዳይሰማህ ፡ ነው ያለኝ ፣ ታዳ ሰው ከዚህ ድረስ ፡ የሚመጣው ለሳቸው ፡ ጀባ ሊል ነው ፡ እንጅ እኛን ለማየት ምስሎህ ፡ ነው እንዴ : አለኝ። ያው እሱ ባለው መንገድ ታረደ ማለት ነው።

بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَنِ الرَّحِيم
      አደራ ብያለሁ ፡ ደግሜ ደግሜ
      ተመሄደ በፊት ፡ በሞት ተቀድሜ
      አፌ ሳይያያዝ ፡ ታምሜ ደክሜ
      አፈር ሳይጫነኝ ፡ ሳይረሳ ስሜ
      ለናንተም ይበጃል ፡ ለኔም ያነው ጥቅሜ
      የማስቀምጠው ስንቅ ፡ ላአኺራ ቀለቤ
      ታላህ ፊት ስጠራ ፡ ስጠየቅ ቀርቤ
      እንዳልደናገር ፡ እንዳይፈራ ልቤ
      በናንተ ዱኣ ላይ ፡ የኔንም ደርቤ

      አላህን ስለምን ፡ ስጣራ አሻቅቤ
      ተመቃብሬ ውስጥ ፡ ተኝቸ አሽልቤ
      መቃብሬ ዙሪያው ፡ በሰው ተከብቤ
      ተደፍቶ ሲያለቅስ ፡ አየሁት ቀርቤ
      አፌ ባይናገር ፡ አዘንኩኝ በልቤ
      እኔ ምን ሀብት አለኝ ፡ ያኖርኩት ቆጥቤ?
      ለሰው የምሰጠው ፡ ለራሴ ጠግቤ
      ትችው ሄድኩኝ አይደል ፡ መች ወሰድኩ ቀንጥቤ


      ሰው ስለሆንኩ አይደል ፡ ጨንቆኝ ተጠብቤ
      ስተቱን ልንገርህ ፡ አንድ ባንድ አስቤ
      ሁሴን ስጠኝ ብለህ ፡ አትምጣ አጠገቤ
      ሰጩም ነሹም አላህ ፡ ልንገርህ ተልቤ
      ተየት አምጥቸ ነው ፡ የመሰጥህ እኔ?
      አላህ ሰጥቶኝ አይደል ፡ እኔስ መለመኔ
      ስጦታው የሚያጠግብ ፡ ያአላህ ነው ወገኔ
      ሰውማ ስው አይደል ፡ ያንተ ቢጤ እንደኔ
      እያለው የሚነፍግ ፡ ጨካኝ አረመኔ
      ወልይ የለም ብየ ፡ አይደለም እኮ እኔ
      የዝህ አይነት ስልጣን ፡ አይገባም ለኔ
      እኔ እኮ ሙቻለሁ ፡ አልቆብኝ ዘመኔ
      ተሞተኩኝ በሁዋላ ፡ ያው አምዋት ነው ጅስሜ
      አላህን ለምነው ፡ አትሁን ቦዘኔ
      አላህኮ ሲሰጥ ፡ ማዝያ አይልም ሰኔ
      ቀጠሮም አይፈልግ ፡ ሰኞና ቅዳሜ
      ውሽት እንዳይመስልህ ፡ ነገርኩህ ብውኔ
      እያረገላችው ፡ እያየሁት ባይኔ
      እኔ አንድ ለማኝ ነኝ ፡ ታንተ አልበልጥም እኔ
      ሁሴን ብለህ ጠርተህ ፡ አትለመን በስሜ
      እንዳይቆጣ አላህ ፡ አዳምጠኝ ወንድሜ
      ናና ዱአ እናድርግ ፡ ቁጭ በእል ታጠገቤ
      አላህ ይሰጠናል ፡ መጀን በል በነቢ
      ዱአ ጠቃሚ ነው ፡ ላንተም ሆነ ለኔ

      እኔ የምለምነው ፡ አላህን ነው ቁሜ
      በጤናየም ብሆን ፡ ታምሜም ደክሜ
      ቢሰጠኝ መርሃባ ፡ ተደስቶ ቀልቤ
      ባጣም አመስግኘ ፡ ቸግሮኝ ተርቤ
      ሰጩ እሱ ነውና ፡ ሀብትም ቢሆን እድሜ
      በሽታም ቢይዘኝ ፡ እሱ ነው ሀኪሜ
      እሱ ነው አዛዡ ፡ በስጋ በደሜ
      ነብዩም ብለዋል ፡ አደራ ኡመሜ
      ታላህ ያራርቃል ፡ ያመጣል ኩነኔ
      ሱጁድና ሶላት ፡ ላአላህ ነው ወገኔ
      ብለው ተናግረዋል ፡ የጦይባው ምስለኔ
      እስቲ አላህን ፍራ ፡ አታጎንብስ ለኔ
      ነቢ ከልክለውት ፡ ማን ፈቀደ ለኔ
      ለሰው እንዳሰግዱ ፡ ረግሚያለሁ እኔ
      ለሞተም ተቀብሮ ፡ ላለም ገና በድሜ
      አቤት ብለህ ስማ ፡ ትዛዙን እንደኔ
      ትዛዙን ተቀበል ፡ አትበል ለምኔ
      እንዳረሳው ብየ ፡ ተሸክሜ አንግቤ
      ለሰው እያስረዳሁ ፡ ልንገርው አንብቤ
      አላሀን መፍራት ነው ፡ ይህ ነው ጥበቤ
      እኔም ተደስቸ ፡ ሌላም ሰው ጠቅሜ
      እሞክራልሁኝ ፡ በምችለው አቅሜ
      ተዛ ወዳ አላልፍም ፡ ይህ ነው ደንበሬ
      ተናግሬያለሁኝ ፡ ውርድ ተራሴ እኔ።
          	***