...ሌላው አማኝ ተውጭ ፡ ሙስሊሙን ሲያየው ድንጋዩን ይመስላል ፡ የምንገዛው እንዳትፈርዱበት ፡ ሰው ስላልገባው...
ሙስሊሞች ፡ ወደ መካ ለሃጅ ይሄዳሉ ፣ ክርስቲያኖች ወደ እይሩሳሌም ይሄዳሉ ፣ አንዳንዱ ክርስቲያን ፡ መካ ማለት ፡ ምን እንደሆነ አይግባውም ፣ እንዳው ሙስሊሙ ፡ የሆነ ደንጋይ ተሳልሞ ፡ የሚመለስ ነው ፡ ይሚመስለው ፣ ጌታው ሸህ ሁሴን ጅብሪል ፡ ስለ መካ ምንነትና ታሪክ ፡ ባጭሩ እንድህ ሲሉ አስቀምጠውታል።
እስልምናን ማውራት ፡ ማስረዳት ለስው ቡዙ አያስቸግርም ፡ ሰው እንድገባው በዟሂር ላየው ሰው ፡ መካ ደንጋይ ነው ውስጡን ግን የሚያውቀው ፡ ያው ኻሊቁ ነው ሌላው አማኝ ተውጭ ፡ ሙስሊሙን ሲያየው ድንጋዩን ይመስላል ፡ የምንገዛው እንዳትፈርዱበት ፡ ሰው ስላልገባው የመጀመሪያው ቤት ፡ ላዐላህ መገዣው የሰው ልጅ ታዐላህ ጋር ፡ የሚያገናኘው አምስት ወቅት ሶላት ፡ ምስገጃ ቂብላው ነቢ ኢብራሂምም ፡ አንድ ጊዜ ሰራው ልጁ አብሮ እይረዳው ፡ እያቀበለው ቡዙ ጊዜ ጠፍቷል ፡ ጎርፍ እየመታው ጣኦት መደርደሪያ ፡ ቁረይሾች አርገው ሰው ይገዛው ነበር ፡ እንደ ፈጣሪው ነቢዩ ሙሐመድ ፡ ሰባብሮ ጣለው ነቢ ሙሐመድም ፡ ሰርቷል እንደዛው ገንዘብ ባያዋጣም ፡ ሀብትም ባይኖረው በጉልበት እረድቷል ፡ ሲሰቀል ጣራው ቁረይሾች ተጣልተው ፡ ነበር ተናንቀው አንድ መላ አመጡ ፡ እንደፋል አርገው ተውስጥ ቁጭ ብለው ፡ ነበር ተፋጠው የመጀመሪያው ሰው ፡ በበር የሚገባው በሚለው ሊስማሙ ፡ እሱ በሚያዘው ሙሐመድ ብቅ አሉ ፡ ተወዳጁ ሰው ገና ነቢ ሳይሆን ፡ ጌታ ሳይሾመው እንኳን መጣህልን ፡ አብረን እንስራው ዙሪያውን ያዙ አሉ ፡ ሽቅብ እናንሳው አንስተው ሰቀሉት ፡ ባንድላይ ሆነው የመካ ታሪኩ ፡ ባጭሩ ይህ ነው። ***